Customize Consent Preferences

We use cookies to help you navigate efficiently and perform certain functions. You will find detailed information about all cookies under each consent category below.

The cookies that are categorized as "Necessary" are stored on your browser as they are essential for enabling the basic functionalities of the site. ... 

Always Active

Necessary cookies are required to enable the basic features of this site, such as providing secure log-in or adjusting your consent preferences. These cookies do not store any personally identifiable data.

No cookies to display.

Functional cookies help perform certain functionalities like sharing the content of the website on social media platforms, collecting feedback, and other third-party features.

No cookies to display.

Analytical cookies are used to understand how visitors interact with the website. These cookies help provide information on metrics such as the number of visitors, bounce rate, traffic source, etc.

No cookies to display.

Performance cookies are used to understand and analyze the key performance indexes of the website which helps in delivering a better user experience for the visitors.

No cookies to display.

Advertisement cookies are used to provide visitors with customized advertisements based on the pages you visited previously and to analyze the effectiveness of the ad campaigns.

No cookies to display.

@ethiopique202 (33)

በጎርጎሮሳውያኑ 2022 እና 2023 በዳውንታውን ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ አካባቢ፤ በአካባቢው ባሉ የንግድ ሰዎች እና ነዋሪዎች ላይ ስጋት የፈጠረ ከፍተኛ ወንጀል ተዘግቦ የነበረ ቢሆንም፣ ይሁን እንጂ ከሰሞኑ ይፋ የተደረገ የባለፈው ዓመት የፖሊስ ሪፖርት በአካባቢው ወንጀል 7.6 ከመቶ መቀነሱን አመላክቷል።


የሞንጎሞሪ ካውንቲ የሦስተኛው ክፍል ኮማንደር የሆኑት ጄሰን ኮኪኖስ ለጋዜጠኞች ጥረታቸው ስኬታማ እየሆነ መምጣቱን አስታውቀዋል።
ሆኖም ኮኪኖስ በመሃል ሲልቨር ስፕሪንግ የሚፈጸሙ ወንጀሎች መቀነስ ቢያሳዩም፤ ነገር ግን አሁን ላይ  የወጣት ታዳጊዎች ወንጀል በከባድ ችግር ነው መሆኑም በካውንቲው በተዘጋጀው መርሃግብር አክለው ተናግረዋል።


በተጨማሪም ኮማንደሩ ታዳጊ ወጣቶቹ መኪና መዝረፍን ጨምሮ፣ የመኪና ላይ የሚፈጸም ስርቆት ፣ እንዲሁም መኪና ይዘው የስርቆት ወንጀል መፈጸም ላይ በተለየ መልኩ ሲሳተፉ እያየን ነው ብለዋል።


ባለፈው ወር የተለቀቀው መረጃ እ.ኤ.አ. ከ2023 ከነበረው አንጻር 2024 ተመሳሳይ ወቅት ሲወዳደር ፣ የመኪና ስርቆት ከ 19 ወደ ስድስት በመውረዳቸው የወንጀል መጠኑ 68% መቀነሱን አመላክቷል።


በተመሳሳይ የዝርፊያ ወንጀል 24 ከመቶ ሲቀንስ፣ ግድያ ወንጀል ደግሞ በመቶ መቀነሱ ተመላክቷል። 


በሞንትጎመሪ ም/ቤት ፕሬዝዳንት የሆኑትና ሳምታዊ መግለጫውን ያዘጋጁት ኬት ስቱዋርት፤ ለወንጀል መቀነሱ በርካታ ምክንያቶችን የጠቀሱ ሲሆን፤ በመሀል ከተማ የመኪና ማቆሚያ ጋራጆች ውስጥ እና አካባቢ ያለው ደህንነት መጨመር፣ የፖሊስ አባላት ከመድረሳቸው በፊት ወንጀል በተፈጸመበት ስፍራ ቀድሞው ጥቅም ላይ የሚውሉ ድሮኖች ለተመዘገበው ለውጥ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸውን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የወጣት ታዳጊ ጥፋተኞች ማረሚያ ጉዳይ ውስብስብ እና ከባድ መሆኑንም ኮማንደሩ አስታውቀዋል።
 
የዲ.ሲ ከንቲባ ሙሪየል ቦውሰር በቅርቡ በዋሺንግተን ዲሲ፤ ወጣት ታዳጊዎች ወንጀል ምርመራ ልዩ ክፍል እንደሚመሰርቱ የተናገሩ ሲሆን፤ ሁኔታው የዲሲ ተጎራባች ለሆነቸው ሜሪላንድ ግዛት ሲልቨር ስፕሪንግ ከተማ አዎንታዊ ውጤት እንደሚኖረውም ተገምቷል።

About Author

ይህን መረጃ ለወዳጅ ዘመዶችዎ ሼር ያርጉት

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.