05/18/2024

የዋሽንግተን ዲሲ ውኃና ፍሳሽ ባለስልጣን ዛሬ አርብ ጃንዋሪ 19 ባወጣው ማስጠንቀቂያ በተወሰኑ የከተማው አካባቢዎች ያሉ ደንበኞች በተለይም የቧንቧ ውኃቸው ግፊት ከተለመደው በተለየ ሃይል ከሌለውና በደንብ የማይወርድ ከሆነ ውኃቸውን አፍልተው እንዲጠቀሙ አስጠንቅቋል።


ማስታወቂያ:- በየጊዜው የምናወጣቸውን መረጃዎች ለማግኘት በፌስቡክና … በቴሌግራም ይከታተሉ:: ለወዳጅ ጏደኞችም ይንገሯቸው::


ይህ ማስጠንቀቂያ በእርግጠኛነት ውኃው መበከሉ ስለተረጋገጠ ሳይሆን ለጥንቃቄ እንደሆነም አክለው ገልጸዋል። በዚህም የተነሳ ይህ የውኃ ኃይል ማነስ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች የቧንቧ ውኃቸውን ሳያፈሉ እንዳይጠቀሙ አሳስቧል።

ውኃ አፍልተው እንዲጠቀሙ የተመከሩ የዲሲ አካባቢዎች
  • ውኃ አፍልተው እንዲጠቀሙ የተመከሩ የዲሲ አካባቢዎች


ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ተገቢውን የላቦራቶሪ ምርመራ አድርጎ የውኃውን ጤነኛነት እስኪያረጋግጥ ድረስም ነዋሪዎች የቧንቧ ውኃ ሳያፈሉ እንዳይጠቀሙ መክሯል።

  • በነዚህ አካባቢዎች ያሉ ነዋሪዎች ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል?
  • በቧንቧ ውኃ የተሰሩ በረዶዎችንና ሌሎች መጠጦችን ያስወግዱ
  • ውኃ ከቧንቧ ሲወርድ ቀለሙን ከቀየረ ንጹህ ውኃ መፍሰስ እስኪጀምር ቧንቧውን ከፍተው ይተዉት
  • የታወቁ የሊድ ምንጮች ካሉ ቀዝቃዛ ውኃ ለሁለት ደቂቃ ያፍሡ
  • ውኃውን ቢያንስ ለ1 ደቂቃ በደንብ ያፍሉትና አቀዝቅዘው ይጠቀሙ
  • የቀዘቀዘውን ውኃ በንጹህና በተሸፈነ ማስቀመጫ ያኑሩት

በዚህ ወቅት ፈልቶ የቀዘቀዘ ውሃ ወይም የታሸገ ውሃ ብቻ ለሚከተሉት አገልግሎቶች ጥቅም ላይ መዋል አለበት፡

  • ለመጠጥ
  • ጥርስ ለመቦረሽ
  • ምግብ ለማብሰል እና ማዘጋጀት
  • ፍራፍሬዎችን እና አትክልቶችን ለማጠብ
  • የሕፃናት ፎርሙላ ለማዘጋጀት
  • በረዶ ለመሥራት
  • ለቤት እንስሳት የመጠጥ ውሃ ለመስጠት
  • በፍጹም የውኃ ማጣሪያ ማሽኖችን ብቻ ተማምነው ውኃ ከማፍላት እንዳይዘናጉ።

ምን ተፈጥሮ ነው ይሄ ማስጠንቀቂያ የወጣው?
አርብ ጃንዋሪ 19 ከሰዓት በኋላ አካባቢ የዲሲ ውሃና ፍሳሽ ዝቅተኛ ወይም ምንም የውሃ ግፊት የለንም ከሚሉ በሰሜን ምዕራብ ዲሲ ውስጥ ከሚኖሩ በርካታ ደንበኞች ጥሪዎችን ተቀበለ። የዲሲ ውሃና ፍሳሽ አሁንም መንስኤውን በማጣራት እና የውኃ ግፊትን ለመመለስ እየሰራ ነው. በስርአቱ ውስጥ ያለው ግፊት በመጥፋቱ ባክቴሪያ ወይም ሌሎች በሽታ አምጪ ተህዋሲያን በማከፋፈያ ስርዓቱ ውስጥ ባሉ ስንጥቆች፣ ስብራቶች ወይም መገጣጠሚያዎች ወደ ውሃ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ።


ማስታወቂያ:- በየጊዜው የምናወጣቸውን መረጃዎች ለማግኘት በፌስቡክና … በቴሌግራም ይከታተሉ:: ለወዳጅ ጏደኞችም ይንገሯቸው::


እንደ ባክቴሪያ፤ ቫይረሶች እና ጥገኛ ተህዋሲያን ያሉ እና ሌሎች በሽታ አምጪ ብክለት እንደ ተቅማጥ፣ ቁርጠት፣ ማቅለሽለሽ፣ ራስ ምታት ወይም ሌሎች ምልክቶችን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ለጨቅላ ሕፃናት፣ ለታዳጊ ሕፃናት፣ ለአንዳንድ አረጋውያን እና በጣም የተዳከመ የበሽታ መቋቋም ሥርዓት ላላቸው ሰዎች የከፋ የጤና አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ።
ከላይ ያሉት ምልክቶች የሚከሰቱት በመጠጥ ውሃ ውስጥ በሚገኙ ማይክሮቦች ብቻ አይደለም. ከእነዚህ ምልክቶች ውስጥ አንዳቸውም ካጋጠሙዎት እና ከቀጠሉ የሕክምና አገልግሎት ያግኙ። ለአደጋ የተጋለጡ ሰዎች ስለ መጠጥ ውሃ ከጤና አጠባበቅ አቅራቢዎቻቸው ምክር ማግኘት አለባቸው።
የዲሲ ውኃ በአሁኑ ሰዓት ውሃው በዚህ ክስተት መበከሉን ምንም መረጃ የለንም ሲል ነገርግን ለጥቃቄ ሲባል ይህ መግለጫ እንደወጣ አስታውቀዋል። በቀጣይም የዲሲ ውኃና ፍሳሽ ባለሞያዎች በተጎዳው አካባቢ የተለያዩ ናሙናዎችን በመሰብሰብ በዕርግጥም ውኃው መበከልና አለመበከሉን የማጣራት ስራ ይሰራሉ። በተከታታይ ሁለት ቀናት በተደረጉ ምርመራዎችም በሽታ አማጭ ጀርሞች ካልተገኙ ማስጠንቀቂያው የሚነሳ ሲሆን ይህም ምናልባት ማክሰኞ ሜይ 30 ሊሆን እንደሚችል መግለጫው አሳውቋል።

የዋሽንግተን ዲሲ ውኃና ፍሳሽ ባለስልጣን ዛሬ አርብ ጃንዋሪ 19 ባወጣው ማስጠንቀቂያ በተወሰኑ የከተማው አካባቢዎች ያሉ ደንበኞች በተለይም የቧንቧ ውኃቸው ግፊት ከተለመደው በተለየ ሃይል ከሌለውና በደንብ የማይወርድ ከሆነ ውኃቸውን አፍልተው እንዲጠቀሙ አስጠንቅቋል።

በተጨማሪም ነፃ የታሸገ ውኃ እደላ በሚከተሉት አድራሻዎች ይኖራል:: ማንኛውም በዚህ ማስጠንቀቂያ በተደረገበት የዲሲ ሰፈሮች የሚኖር ሰው በተጠቀሱት አድራሻዎችና ሰአት ብመሄድ የታሸገ ውኃ መውሰድ ይችላል ተብሏል

Catholic University of America, Raymond A. Duford Athletic Center (8:30-11:30pm)
4400 John McCormack Rd NE, Washington, DC 20011

University of the District of Columbia Building 44 (9:00-11:30pm)
4200 Connecticut Ave NW, Washington, DC 20008
3000 Block Van Ness Street NW and International Drive/ Connecticut Ave NE


ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚኖሩ ወዳጅ ዘመዶች ካሏችሁ ራሳቸውን ከበሽታ እንዲጠብቁ ይህን መረጃ አጋሯቸው።

About Author

ይህን መረጃ ለወዳጅ ዘመዶችዎ ሼር ያርጉት