TR Bridge Rehab_Flyer

በቀን በአማካይ እስከ 95 ሺህ መኪኖችን የሚያስተናግደውና በዲሲና በቨርጂንያ ማዕከላዊ መገናኛ በመሆን የሚያገለግለው የቲዎዶር ሩዝቬልት ድልድይ ከዚህ ሳምንት ጀምሮ 127 ሚልየን ዶላር የሚያወጣ መሰረታዊ ጥገና ሊደረግለት እንደሆነ ተነግሯል።
ይህን ፕሮጀክት በዋናነት የሚያስተዳደረው የዲሲ ትራንስፖርት ዲፓርትመንት ሲሆን ፕሮጀክቱ 4 ዓመት ይፈጃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተነግሯል።
ይህ ፕሮግራም ሲጀመር በድልድዩ በስተሰሜን ላይ የነበረው መረማመጃ የሚሰፋ ሲሆን ይህም ለዕግረኞችና ለባለ ሳይክሎች ተጨማሪ ቦታ ይሰጣል ተብሏል። በተጨማሪም የትራፊክ መቆጣጠሪያዎችና ምልክቶች የሚደረጉ እንደሚሆን በመግለጫው ተነግሯል።
የዲሲ ትራንስፖርት ዲፓርትመንት ይህ ጥገና የድልድዩን እድሜ ከግምት በማስገባት ወሳኝ እንደሆነ ተናግሯል። ይህ ጥገና በሚከናወንባቸው 4 አመታትም አሽከርካሪዎች ሊስተጓጎሉ እንደሚችል የተነገረ ሲሆን የመንገድ መዘጋት፤ የመስመር መዘጋትና የመሳሰሉት ሊኖሩ እንደሚችሉና ሀይዌይ 66ና በአካባቢው ላይ ባሉ መንገዶችም የትራፊክ መጨናነቅ ሊያስከትል እንደሚችል ተነግሯል።
በዚህ ወቅትም አሽከርካሪዎች የህዝብ ትራንስፖርት እንዲጠቀሙ እንደሚመከር አስታውቀዋል። የዚህን የድልድይ ጥገና ወጪ 90 ከመቶው በፌደራል መንግስቱ የሚሸፈን ሲሆን ቀሪው 10% ደሞ በዲሲ መንግስት እንደሚሸፈን ተነግሯል።

About Author

ይህን መረጃ ለወዳጅ ዘመዶችዎ ሼር ያርጉት

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.