Add a heading

Credit: Fairfax County Park

በ2025 በካውንቲው ባሉ 10 ፋርመርስ ማርኬቶች ላይ ምርቶቻቸውን ይዘው መቅረብ የሚፈልጉ የምግብና ምግብ ነክ ምርቶችን የሚያመርቱ ነጋዴዎችን ማመልከቻቸውን መቀበል ሊጀምር እንደሆነ የፌርፋክስ ካውንቲ ፓርክ አስታወቀ፡፡ በማስታወቂያው ላይ እንደተገለጸው በፌርፋክስ ካውንቲ 125 ማይል ራዲየስ ውስጥ የሚገኙ ማናቸው የምግብ አምራቾች መሳተፍ ይችላሉ፡፡

ለምሳሌ ዲሲ ከፌርፋክስ ካውንቲ በ 20 ማይል ርቀት አካባቢ ላይ ይገኛል፡፡ ባልቲሞር በ 40 ማይል፤ ሪችመንድ በ100 ማይል አካባቢ ፤ ሀሪስበርግ ፔንሳልቬንያ በ110 ማይል አካባቢ እንዲሁም ፍሬድሪክስበርግ ቨርጂንያ በ50 ማይል ርቀት አካባቢ ላይ ይገኛሉ፡፡

በዚህ ፋርመርስ ማርኬት ላይ ለመሳተፍ አመልካቾች ይዘውት የሚቀርቡትን የምግብ/መጠጥ አይነት ራሳቸው የሚያመርቱት መሆን አለበት፡፡ በዚሁ አካባቢ ካሉ ግብዐቶች ከተመረተ ደሞ ይበልጥ ተመራጭ ይሆናል ተብሏል፡፡

በዚህ ፕሮግራም መሳተፍ ለሚፈልጉና ምርቶቻቸውን በፌርፋክስ ካውንቲ ባሉ 10 የፋርመር ማርኬቶች በመሸጥ ተጨማሪ ገቢ ማግኘት የሚፈልጉ ሰዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና የጥያቆእዎች መመለሻ ፕሮግራም ፓርኩ ለጃንዋሪ 14 አዘጋጅቷል፡፡ በዚህ ቨርቿል የግንዛቤ ማስጨበጫ ለመሳተፍ ይህንን ተጭነው ይመዝገቡ፡፡ መረጃውን ያገኘነው ከካውንቲው ድረ ገጽ ነው፡፡

About Author

ይህን መረጃ ለወዳጅ ዘመዶችዎ ሼር ያርጉት

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.