463157840_537043429080024_2486110222813395184_n

የስሚዞንያን ናሽናል ዙ ማክሰኞ ኦክቶበር 15 ሁለት ፓንዳዎችን ከቻይና ተረክቦ እንደነበር ይታወቃል። ከአመት በፊት 2 ፓንዳዎች የውሰት ዘመናቸው በማለቁ ወደ ቻይና ተመልሰው ነበር:: ከ11 ወራት በሁዋላም ባሳለፍነው ኦክቶበር ባኦ ሊ እና ቺንግ ባኦ የተባሉ ፓንዳዎች ወደ መካነ አራዊቱ ተቀላቅለው ነበር።

ላለፉት ሳምንታት ታዲያ የመካነ አራዊቱ ባለሞያዎች እኚህን ፓንዳዎች ለዲሲ አየር ሲያለማምዷቸው የቆዩ ሲሆን በተያዘላቸው ቀጠሮ መሰረትም ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ፓዳዎቹ ለህዝብ ምልከታ ክፍት ይሆናሉ። ምንም እንኳ ወደ ናሽናል ዙ ለመግባት ክፍያ ባያስፈልገውም ጎብኚዎች ነጻ የመግቢያ ትኬት ከመሄዳቸው በፊት መቁረጥ እንዳለባቸው ተጠቁሟል። ቲኬቱን ለመቁረጥ ይህን ይጫኑ።

የፓንዳዎቹን ለህዝብ ክፍት መሆን አስመልክቶም የዲሲ ሜትዎ የመታሰቢያ የሜትሮ ካርድ አሳትሟል።

በቦታው በአካል መገኘት የማይችሉ ደሞ ኦንላየን በቀጥታ የሚሰራጩ ቪዲዮችን ማየት እንደሚችሉ የመካነ አራዊቱ አስተዳዳሪዎች አስታውቀዋል።

ይህን ተጭነው ፓንዳዎቹን በቀጥታ ይመልከቱ

About Author

ይህን መረጃ ለወዳጅ ዘመዶችዎ ሼር ያርጉት

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.