IMG_9880

ፕሬዘደንት ትራምፕ ከተመረጡ በኋላ ከወሰዷቸው እርምጃዎች አንዱ በሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ ላይ ግዙፍ መዋዕለ ንዋይ ለማፍሰስ አቅደዋል። ምንም እንኳ የሰውሰራሽ አስተውሎት ጥቅም እና ጉዳት እያከራከረ ቢሆንም በሀገረ-አሜሪካ የሰውሰራሽ አስተውሎት መሠረተ ልማትን ለመገንባት የ500 ቢሊዮን ዶላር በጀት መድበዋል ። መርሃ ግብሩ «ስታርትጌት» ይባላል። በዚህ ፕሮጀክትም ሶስት ትልልቅ ተቋማት ይጣመራሉ። የቻትጂፒቲ ጠንሳሽ ኦፕን ኤ.አይ.; ሶፍት ባንክና ኦራክል ኮርፖሬሽን ይህንን ፕሮጀክት ለመምራት ከፕሬዘደንት ትራምፕ ፍቃድ ተሰቷቸዋል።


ፕሬዘደንት ትራምፕ ይህን ባወጁበት ወቅት አሜሪካ የሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ ዋና መናኸሪያ እንደምትሆንና በአለም ላይም በዘርፉ ቀዳሚ እንደምትሆን ተናግረው ነበር።

ይህ ከሆነ ከቀናት በኋላ ታዲያ የቻይናው ጀማሪ የንግድ ተቋም የሆነው ዲፕሲክ የተባለ የሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ እንደፈበረከና እስካሁን ለህዝብ ከቀረቡት የሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ መተግበሪያዎች ሁሉ የላቀ እንደሆነ ተናግረው ነበር። ይህንን መተግበሪያ ለመስራትም ከ10 ሚልየን ያነሰ ወጪ እንዳስወጣቸው ጠቁመዋል።


ይህን ተከትሎም ይህ የሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ መተግበሪያ በአሜሪካ ቀዳሚው ዳውንሎድ የሚደረግ መተግበሪያ ሆኗል። የዲፕሲክ ባለቤቶች ታዲያ የዚህን መተግበሪያ ኮድ ለአለም በሙሉ ክፍት ያደረጉት ሲሆን ይህም የአሜሪካንን የሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ የበላይነት ህልም መና ሊያስቀረው እንደሚችል በርካቶች ይተነትናሉ።

የዚህን ዜና ተከትሎም በሰው ሰራሽ አስተውሎት/AI/ ላይ አተኩረው የሚሰሩ እንደ ኦራክልና ንቪዳ ያሉ የቴክኖሎጂ ስቶክ ማርኬት ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ወድቋል።

Image: Robinhood


የዲፕሲክ ባለቤቶች ዛሬ ሰኞ ጃንዋሪ 27 ባወጡት መግለጫ በመተግበሪያቸው ላይ አዲስ ተመዝጋቢዎችን መቀበል እንዳቆሙ ተናግረዋል። ይህ የሆነበት ምክንያት ደሞ ከፍተኛ የሆነ የሳይበር ጥቃት ስለደረሰባቸው እንደሆነ ተናግረዋል::
መረጃውን ያገኘነው ከሬውተርስ ነው።

About Author

ይህን መረጃ ለወዳጅ ዘመዶችዎ ሼር ያርጉት

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.