ማህበራዊ

በአገር አቀፍ ደረጃ ትልቅ አጀንዳ የነበረውና በርካታ ኢትዮጵያውያንንና ኤርትራውያን በተቃውሞ የተሳተፉበትን የሞንጎምሪ ካውንቲ የትምህርት ከሪኩለምን በተመለከት የወላጆች ክስ በስር...
የፌደራል አስቸኳይ ይግባኝ ለመስማት ከሰሞኑ ቀጠሮ ይዞ የነበረው የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ መንግስት በስህተት ዲፖርት ያደረገውን ሰው እንዲመልስ ውሳኔውን...
በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ የሞንጎመሪ ካውንቲ ፖሊስ በኢሚግሬሽን አስገዳጅ አፈጻጸም  ስራዎች ውስጥ በመግባት  ህገወጥ ስደተኞችን ማሰስ እና ማሰር ውስጥ እንደማይሳተፍ የካውንቲው የሥስተኛ እዝ  አዛዥ የሆኑት ጄሰን ኮኪኖስ በዚህ ሳምንት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። ኮኪኖስ አቋማችን አይለወጥም ብለዋል።  በተመሳሳይ የሞንጎመሪ ካውንቲ ም/ቤት  ፕሬዝዳንት  ኬት  ስቱዋርት  የኮኪኖስ  አቋም  ደግፈው ያንጸባረቁ  ሲሆን፤  በዚሁ ሳምንታዊ አጭር መግለጫ ላይ፣  ማንኛውም  ሰው – ምንም ዓይነት የኢሚግሬሽን ሁኔታ ላይ ቢሆንም ሊያሳበው የሚገባው የህዝብ ደህንነት ስጋት ብቻ መሆኑን በመግለጽ ነዋሪዎች ሳይፈሩ የሚጋጥሟቸውን የህግ ጥሰቶች በአግባቡ እንዲያመለክቱ  አሳስበዋል።  ኮኪኖስ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ በቅርቡ በሎንግ ብራንች፣ ብዙ ስደተኞች ባሉበት ሰፈር ውስጥ በተደረገ የማኅበረሰብ ስብሰባ ላይ ተሳትፈው እንደነበር በመግለጽ ሰዎች ያለፍርሃት ከፖሊሶች ጋር ስላለባቸው ስጋት ሲነጋገሩ ማየታቸው እና ያለው መቀራረብ እንዳሰደነቃቸው ገልጸዋል። የሞንጎመሪ ካውንቲ ፖሊስ ዲፓርትመንት የዩናይትድ ስቴትስ የኢሚግሬሽን እና ጉምሩክ አስፈጻሚ አይስ የአካባቢ ህግ አስከባሪ መኮንኖችን እንዲጠቀም የሚፈቅደውን የኢሚግሬሽን ስምምነት 287(g) ውስጥ ተሳታፊ አይደለም። የካውንቲው ፖሊስ ሦስተኛ እዝ ክፍል ሲልቨር ስፕሪንግ፣ ዋይት ኦክ እና በርተንስቪልን አካባቢዎችን የሚያጠቃልል ነው። በተያያዘ የቨርጂንያ ገቨርነር የስቴት ፖሊሶች እንዲተባበሩ...
የዩናይትድ ስቴትስ የአገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት ዛሬ ረቡዕ ኤፕሪል 9 ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው ከሆነ የአሜሪካ የስደተኞች ቢሮ (USCIS)...
በጎርጎሮሳውያኑ 2022 እና 2023 በዳውንታውን ሲልቨር ስፕሪንግ ሜሪላንድ አካባቢ፤ በአካባቢው ባሉ የንግድ ሰዎች እና ነዋሪዎች ላይ ስጋት የፈጠረ ከፍተኛ...

Sign In

Register

Reset Password

Please enter your username or email address, you will receive a link to create a new password via email.